የምንፈልገውን አካባቢ በመምረጥ የEIRP ቫሊዩ ስንት እንደሆነ እናያለን፡፡
ለምሳሌ አዲስ አበባ በኢትዮጵያ መሃል አካባቢ ነው የምትገኘው፡፡
የኢትዮፕያን ማፕ ከስር ተመልከቱ፡፡
ከዛ ደግሞ ከላይኛው ፖስት ላይ ያለውን ፉት ፕሪንት ልብ በሉ፡፡
አዲስ አበባን አርባሰባት EIRP ነክቷት ያልፋል፤ አይደል?
ከሞላ ጎደል ስለዚህ በ አርባስድስት እና አርባሰባት ወይም አርባስምንት ዉስጥ ናት ማለት እንችላለን፡፡
ያም ማለት ለአርባሰምንት ከ ስልሳ እስከ ሰባአምስት ሴሚ የሆነ ሳህን በቂ ነው፡፡
ለአርባስድስት ደግሞ ከሰባ አምስት እስከ ዘጠና አምስት የሆነ ሳህን ይበቅል እንደማለት ነው፡፡
እስኪ ደግሞ አሳይታን እንውሰድ(አሳይታ አፋር ዉስጥ ነው በሰሜን ምስራቅ ኢትዮጵያ ከጅቡቲ ጎን)
ከላይ ፍትፕሪንቱ ላይ እንደምታዩት አሳይታ ከአርባስምንት በላይ EIRP(dbw) ነው የምታገኝው፡፡
ስለዚህ ከስልሳ እስከ ሰባአምስት ሴሚ የሚሆን የሳህን መጠን በቂ ነው ማለት ነው፡፡
ጂማ፣ሃዋሳ፣ሻሸመኔ፣ጎባ፣ጎዴ የመሳሰሉት ከተሞች ከአርባሰባት በታች EIRP(dbw) ነው የሚያገኙት፡፡
ባህርዳር፣ደሴ፣ጎንደር፣መቐሌ ደግሞ ከ አርባሰባት በላይ EIRP(dbw) ያገኛሉ፡፡
ከላይኛው ሰንጠረዥ እንደምታዩት የEIRP(dbw) መጠን ሲጨምር በአነስተኛ ሳህን መጠቀም እንችላለን እንደማለት ነው፡፡
በአጠቃላይ የሌሎችንም ሳታላይቶች ፉት ፕርንት አይተን እንደምንረዳው በደቡብ እና ደቡብ ምስራቅ አካባቢዎች አነስተኛ የEIRP(dbw)
ሽፋም አላቸው፡፡ ያም ማለት መጠኑ ተለቅ ያለ ሳህን በእነዚህ አካባቢዎች ያስፈልገናል ማለት ነው፡፡
[You must be registered and logged in to see this image.]መረጃው ጠቃሚ ሆኖ ከታዮት በስተቀኝ በኩል የሚታየዉን ፕላስ ጫን ያድርጉ!